ኢየሱስ ሌሎችን በጥበብ እና በእውነት እንድንወድ አስተምሮናል፦
ክርስቲያናዊ ፍቅር ማለት ሰዎችን ሁሉ ማስደሰት ማለት አይደለም። ኢየሱስ ለሰዎች ርኅራኄን አሳይቷል ፤ ነገር ግን መቼ መራቅ እንዳለበት ፣ እውነትን መናገር እንዳለበት እና ለአባቱ ዓላማ ታማኝ ሆኖ መኖር እንዳለበት ያውቅ ነበር።
ሌሎችን መውደድ ማለት እግዚአብሔር የሰጣችሁን ማንነት እና ጥሪ መተው ማለት አይደለም።
ፈቃደኛ የሆነ ልብ አሁንም ጤናማ ወሰን (Boundary) ያስፈልገዋል፦
አንዳንድ ሰዎች ፍቅር ማለት ለሁሉም ነገር "እሺ" ማለት ፣ የሁሉንም ሸክም መሸከም ወይም ሌሎች ሁልጊዜ ከእነርሱ እንዲወስዱ መፍቀድ ይመስላቸዋል።
ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ በጥበብ እንድንወድ ያስተምረናል። ጌታ ኢየሱስ እንኳ ለመጸለይና ከአባቱ ጋር ጊዜ ለማሳለፍ ፈቀቅ ይል ነበር ፤ ይህም ሌሎችን መንከባከብ መንፈሳዊ ጤንነታችንንም መንከባከብ እንደሚጠይቅ ያሳየናል።
ክብራችሁ የሚመጣው በእግዚአብሔር ዘንድ ከተሰጣችሁ ቦታ እንጂ በሰዎች ተፈላጊ ከመሆን አይደለም፦
ማንነታችንን ሌሎችን በመርዳት ላይ ብቻ ስናደርግ ፣ የሰዎችን ፍቅርና ተቀባይነት ለማግኘት ስንጥር ልንደክም እንችላለን። ነገር ግን እግዚአብሔር ቀድሞውኑ ዋጋችሁን ያውቃል። የተጠራችሁት የሰዎችን ማረጋገጫ ለመፈለግ ሳይሆን በፍቅር ላይ ተመስርታችሁ ሌሎችን እንድታገለግሉ ነው።
እውነተኛ ፍቅር በእግዚአብሔር ውስጥ ተተክሎ ሳለ ክርስቶስን ያንጸባርቃል፦
የፍቅር ታላቁ አብነት ከአባቱ ፈቃድ ሳይወጣ ራሱን ሙሉ በሙሉ አሳልፎ የሰጠው ጌታ ኢየሱስ ነው። እኛም በልግስና እንድንወድ ፣ በነጻ እንድናፈቅር እና በጥሩ ታማኝነት እንድናገለግል ተጠርተናል ፤ ነገር ግን የመጀመሪያውና ዋናው ኃላፊነታችን ከእግዚአብሔር ጋር ቅርብ ሆኖ መኖር መሆኑን ማስታወስ አለብን።
0 Comments